ካህናት
- አባ ገብረጊዮርጊስ ካሳዬ :- አስተዳዳሪ
- ቀሲስ ዶ/ር ኃይለኢየሱስ አለባቸው
- ቀሲስ ስመኘው ጌትዬ:- ስብከተ ወንጌል እና መንፈሳዊ ትምህርት ክፍል ኃላፊ
- ዲ.ን ተሻለ ቢያዝን
- ዲ.ን ሳምሶን
- ዲ.ን ተስፋልደት
- ዲ.ን አብርሃም
የስቶክሆልም መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የመተዳደርያ ደንብ ረቂቅ ከግንቦት 2009 ዓ.ም ጀምሮ ሥራ ላይ እንዲውል ተደርጓል። የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያኗን የአገልግሎት አድማስ ማስፋት እና ማስቀጠል እንዲቻል ዋናው ቃለ ዓዋዲ በሚገባ ተጠብቆ፤ ይህ አጥቢያው የሚመራበት የመተዳደሪያ ደንብ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና እና ትውፊት ሳይወጣ አጥቢያው የተመሠረተበትን ሀገር አሠራር እና ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ተዘጋጅቷል።
የመተዳደርያ ደንቡን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
{flike}{plusone}
የስቶክሆልም መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የመተዳደርያ ደንብ ረቂቅ በሀ/ስብከቱ ታይቶ እና ታርሞ በሥራ ላይ እንዲውል ተፈቀደ።
የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያኗን የአገልግሎት አድማስ ማስፋት እና ማስቀጠል እንዲቻል ዋናው ቃለ ዓዋዲ በሚገባ ተጠብቆ፤ ይህ አጥቢያው የሚመራበት የመተዳደሪያ ደንብ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና እና ትውፊት ሳይወጣ አጥቢያው የተመሠረተበትን ሀገር አሠራር እና ነባራዊ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ ተዘጋጅቷል። የደብሩ ሰበካ አስተዳደር ጉባኤ የመተዳደርያ ደንቡን ረቂቅ ለአጥቢያው ማኅበረ ምእመናን ጠቅላላ ጉባኤ አቅርቦ ሠፋ ያለ ውይይት እንዲካሄድበት ካደረገ በኋላ የተሰጡ አስተያየቶች እና ማሻሻያዎች ተካተው የተሻሻለውን ረቂቅ ሀገረ ስብከቱ በጉባኤ አይቶ እና አስተካክሎ እንዲያጸድቀው መላኩ ይታወሳል። በዚህም መሠረት ሀ/ስብከቱ ረቂቅ ደንቡን ተመልክቶ አስፈላጊውን ማሻሻያ ካደረገ በኋላ በሥራ ላይ እንዲውል ፈቅዷል።
እሑድ ሰኔ 11 ቀን 2009 ዓ.ም. ከሥርዓተ ቅዳሴ በኋላ በደብሩ አስተዳዳሪ በመላክ ብርሃን አባ ገ/ጊዮርጊስ አማካይነት በተነበበው የሀ/ስብከቱ የመሸኛ ደብዳቤ ”… ደንቡ በሥራ ላይ እንዲውል የተፈቀደ መሆኑን እየገለጽን የደብሩ ሰላምና የሕዝበ ክርስቲያኑ ፍቅር፣ አንድነት እንደተጠበቀ በደብሩ የሚሰጠው ማንኛውም መንፈሳዊ አገልግሎት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከአደራ ጋር እናሳስባልን።” ሲሉ የመላው አውሮፓ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሙሴ አባታዊ መመሪያ አስተላልፈዋል።
በመ/ጸ/ቅ/ስ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤት ታዳጊዎች አመታዊ የኪዳነምሕረት በዓል አከበሩ
የካቲት 11 ቀን 2009 ዓም የኪዳነምሕረት ማህበር አባላት ወይንም የቤተ ክርስትያኑ ሰንበት ት/ቤት ታዳጊዎች በደመቀ ሁኔታ አመታዊ የኪዳነምሕረትን በዓል አክብረዋል። የአገሪቱ ሁኔታ የኪዳነምሕረትን በዓል በቀኑ ለማክበር አስቸጋሪ ቢያደርገውም የማህበሩ አባላት ቀደም አድርገው ቅዳሜ ቀን የካቲት 10 ላይ በሰፊው አክብረዋል። በአሉንም በደብሩ አስተዳዳሪ በአባ ገብረ ጊዮርጊስ ጸሎትና ቡራኬ የተጀመረ ሲሆን፤ በዝግጅቱም ላይ በታዳጊዎች የተዘጋጁ ግጥም፣ ጭውውት፣ ድራማና ታሪክ እንዲሁም ውዳሴ ማርያምን በዜማ ቀርቧል።
ለታዳሚው ጥሩ መልክት ካስተላለፉት መካከል በድራማ መልክ የቀረበው ከሞት ጋር የተደረገ ውይይት የሚለው አንዱ ነበር በድራማው ላይ ሞት ስለትውልድና ዕድገቱ ሲጠየቅ የሚከተለውን ብሎ ነበር ̋አያቴ ምኞት፤ አባቴ ቃየል፤ እናቴ ደግሞ ሐጢያት ይባላሉ። የተወለድኩት 5500 ዓመት ከክርስቶስ ልደት በፊት ነው ከዚያ ወዲህ በመላው ዓለም እየተዘዋወርኩ የሰውን ልጅ ከዚህ ዓለም ወደዚያኛው ዓለም ሳጐዘው እኖራለሁ ̋፟ ብሎ መልሶ ነበር፣ በተጨማሪም የስሙ ትርጉም፣ የት እንደሚኖር፣ የተደሰተባቸው ቀናት፣ ዛሬ በምን እንደሚደሰት፣ ስለ ወገኖቹ፣ ሰዎችን እንዴት እንደሚመለከታቸው፣ ሰዎች ለምን እንደሚፈሩት እናም ስለ አስቂኝ ገጠመኞቹ በድራማው ተዳስሰው ነበር።
ስለ ታቦት በቀረበው ጭውውት ላይ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ እና መናፍቅ ያደረጉትን ውይይት ስለ ታቦት ምንነት በዝርዝር እና በደንብ አስተምረዋል። ስለቅዱሳን ታሪክ በመነባንብ መልክ የአባ ኢየሱስ ሞዓ ወይንም የመጀመርያው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን ዩኒቨርሲቲ መሥራች ታሪክ ተተርኳል። እንዲሁም በጣም አስደሳች እና አስገራሚ የነበረው የህፃናት ሃይማኖታዊ ጥያቄና መልስ ውድድር ተካሂዶ ሁሉም ህፃናት ምንም ጥያቄ ባለመሳሳት የተዘጋጀላቸውን ሽልማት ወስደዋል።
በመጭረሻም ከታዳሚዎች ገንቢ አስተያየትን ለማሕበሩ አባላት ተሰጥቶ የፕሮግራሙ መጠናቀቂያ ሆኗል።
============================
ቅዳሜ ሚያዚያ 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ከ14:00 ሰዓት ጀምሮ
(Lör. Apr. 23, 2016) Kl. 14:00
ቦታ:- Nacka/Centralplan,
Värmdövägen 622, 132 41 Saltsjö-boo
Buss: 422, 444, 471, från Slussen
============================
በመርሐ ግብሩ:- ወቅቱን ያገናዘቡ የበገና መዝሙራት፥ ሥነ ግጥም፥ ስብከተ ወንጌል፥ መዝሙር በሕጻናት እና በሰ/ትቤቱ መዘምራን ይቀርባሉ።
በሰዓቱ በመገኘት የበረከቱ ተሳታፊ ይሁኑ።
============================
አዘጋጅ:- በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ሰ/ምዕ/አውሮፓ አህጉረ ስብከት የስቶክሆልም መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት
{flike}{plusone}
”ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው።” መዝ. 59፥4
ሚያዝያ 6 ቀን 2007 ዓ.ም.
ትንሣኤ የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡
መገኛ ቃሉም ተንሥአ = ተነሣ የሚለው ግሥ ይሆናል፡፡
ትንሣኤ ማለት = መነሣት፣ አነሣሥ፤ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡ ትንሣኤ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲተረጐም አምስት ክፍሎች አሉት፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ይህን ይጫኑ
መጋቢት 29 ቀን 2007 ዓ.ም.
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓዋጅ ከሚጾሙት አጽዋማት መካከል ዐቢይ ጾም፤ ጾመ ኢየሱስ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ አሁን በጾሙ መጨረሻ ሳምንት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሕማምና ሥቃይ እንዲሁም እንግልት በምናስብበትና የጨለማውን ዘመን በምናስታውስበት ጊዜ /ሰሙነ ሕማማት/ ላይ እንገኛለን፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ይህን ይጫኑ