በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ፣ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ

በአባ ገ/ጊዮርጊስ ካሳዬ

ግንቦት 21 2006 ዓ.ም.

ዕርገት የሚለው ቃል መገኛው የግእዝ ቋንቋ ሲሆን፡-

መገኛ ቃሉም “ዐረገ” = “ከፍ አለ፣ ወጣ” የሚለው የግዕዝ ግሥ ይሆናል።

ዕርገት ማለት ደግሞ = ከፍ ማለት፣ ወደ ላይ መውጣት ማለት ነው።

በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ዕርገት ሁለት ዓይነት ነው፡-

የኅሊና ዕርገት እና

የአካል ዕርገት

Read more

የትንሣኤው ትርጉም በዓሉና አከባበሩ

ከሊቀ ትጉሃን ኀ/ጊዮርጊስ ዳኘ
በጠ/ቤተ ክህነት የዕቅድና ልማት መምሪያ ምክ/ሓላፊ

  • «ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡

  •  መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግሥ ይሆናል፡፡

  • «ትንሣኤ» ማለት ታዲያ = መነሣት፣ አነሣሥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡

  •  «ትንሣኤ» በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲተረጐም ዐምስት ክፍል አለው፡፡

  • «ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡

  • መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግሥ ይሆናል፡፡ Read more

ቀዳም ሥዑር

ቅዳሜ፡

ቀዳም ሥዑር ይባላል፡፡ በዚች ዕለች ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው ቅዳሜ ትባላለች፡፡
የማትጾመዋ ቅዳሜ ስለምትጾም ስዑር /የተሻረች/ ተብላለች በዓል መሻርን አይመለከትም በቀዳም ሥዑር  ሌሊት ሥርዓቱ የሚጀመረው በመኀልየ ሰሎሞን ምንባብ ነው፡፡ ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጥዋት አቡን መዋሥዕት ውዳሴ ማርያም ዜማ ተደርሶ ወለመልአከ ሕይወትሰ ሰቀልዎ በሚለው ሰላም ይጠናቀቃል፡፡በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጨሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡

ለምለም ቅዳሜ፡- ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ በዚህ ተሰይሟል፡፡ ቀጤማውንም ምእመናን እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል፡፡
በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል /ቃለዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሠሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡ 
የቀጤማው አመጣጥና ምስጢርም ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቀጤማ ይዛ በመግባት ነው፡፡
ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት ካህናት ቄጠማ ይዘው ምእመናንን ያበሥሩበታል፡፡ Read more

ጸሎተ ሐሙስ

በሊቀ ጠበብት ሐረገወይን አገዘ

ጸሎተ ሐሙስ ነቢያት በሀብተ ትንቢት በመንፈሰ ትንቢት ‹‹እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት›› /መዝ. 117፥24/ በማለት ትንቢት የተናገሩላት በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ትላልቅ የተባሉ ምሥጢራት የተፈጸሙባት ዕለት ናት፡፡

“እግዚአብሔርም በግብጽ አገር ሙሴንና አሮንን እንዲህ ብሎ ተናገራቸው ይህ ወር የወሮች የመጀመሪያ ይሁናችሁ የዓመቱም የመጀመሪያ ወር ይሁናችሁ፡፡ ለእስራኤል  ልጆች ሁሉ ተናገሩ፥ በሉአቸውም በዚህ ወር በአሥረኛው ቀን ሰው ሁሉ ለአባቱ ቤት አንድ ጠቦት ለአንድ ቤትም አንድ ጠቦት ይውሰድ፡፡ የቤቱ ሰዎች ቁጥርም ለጠቦቱ የማይበቃ ቢሆን እርሱና ለቤቱ የቀረበው ጎረቤቱ እንደነፍሶቻቸው ቁጥር አንድ ጠቦት ይውሰድ እያንዳንዱም እንደሚበላው መጠን ከጠቦቱ ይካፈሉ፡፡ የእናንተ ጠቦት ነውር የሌለበት የአንድ ዓመት ተባት ይሁን ከበጎች ወይም ከፍየሎች ውሰዱ በዚህም ወር እስከ አሥራ አራተኛ ቀን ድረስ ጠብቁት፡፡ የእስራኤልም ጉባኤ ሁሉ ሲመሽ ይረዱት፡፡ ከደሙም ወስደው በሚበሉበት ቤት ሁለቱን መቃንና ጉበኑን ይቀቡት፡፡ በእሳት የተጠበሰውን ሥጋውንና ቂጣውን እንጀራ በዚያች ሌሊት ይብሉ ከመራራው ቅጠል ጋር ይበሉታል ጥሬውን በውኃ የበሰለውን አትብሉ ነገር ግን ከራሱ ከጭኑ ከሆድ ዕቃው ጋር በእሳት የተጠበሰውን ብሉት ከእርሱም እስከ ጧት አንዳች አታስቀሩ እስከ ጧትም የቀረውን በእሳት አቃጥሉት ወገቦቻችሁን ታጥቃችሁ፥ ጫማችሁን በእግራችሁ በትራችሁንም በእጃችሁ አድርጋችሁ እንዲህ ብሉት፡፡ ፈጥናችሁም ትበሉታላችሁ እርሱ የእግዚአብሔር ፋሲካ ነው፡፡ እኔም በዚያች ሌሊት በግብጽ አገር አልፋለሁ… ይህም ቀን መታሰቢያ ይሁንላችሁ፥ ለእግዚአብሔርም በዓል ታደርጉታላችሁ ለልጅ ልጃችሁም ሥርዓት ሆኖ ለዘላለም ታደርጉታላችሁ /ዘዳ.12፥1-15/፡፡

Read more

ሰሙነ ሕማማት

በዲያቆን ኅሩይ ባየ

የዐቢይ ጾም የመጨረሻው ሳምንት ሰሙነ ሕማማት እጅግ የተናፋቂና ተወዳጅ ሳምንት ነው፡፡ በእነዚህ 6 ዕለታት የአምላካችንን ሕማም መከራና ስቃይ አብዝተን የምናዘክርባቸው ዕለታት ናቸው፡፡ የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸዋትዎ መከራ በዓመት አንድ ጊዜ በተወሰኑ ዕለታት የሚታሰብ ሳይሆን በሕይወት ዘመናችን ሁሉ የምናስበው የዕድሜ ልክ ስጦታ ነው፡፡ ይኸን ሲያስታውስ ሐዋርያው እንዲህ ይላል “ይህን እንጀራ በበላችሁ ጊዜ ይህንንም ጽዋ በጠጣችሁ ጊዜ ሁሉ ጌታ እስኪመጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና” 1ቆሮ.11፥26፡፡ እውነት ነው ከእግዚአብሔር ጋር አንድ የምንሆንበትን በዕለተ ዐርብ ስለ እኛ ፍቅር የተቆረሰውን ቅዱስ ሥጋና የፈሰሰውን ክቡር ደም ስንቀበል ሕማሙን ሞቱን ትንሣኤውን እናስባለን፡፡ ለዚህም ነው ቅዱስ ጳውሎስ “የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሥጋችን ይገለጥ ዘንድ ሁል ጊዜ የኢየሱስን መሞት በሥጋችን ተሸክመን እንዞራለን፡፡” 2ቆሮ.4፥10 በማለት ሞቱን ማሰብ የሕይወታችን መሠረት እንደሆነ የጻፈልን፡፡

በእርሱ ሞት እኛ ሕይወትን እንድናገኝ ሞቱ በቅዱሳን ሕይወቱ ደግሞ ለእኛ ሆነልን 2ቆሮ.4፥12፡፡ ስለዚህ ዘለዓለማዊ ሕይወትን የሰጠንን እርሱን እናመሰግነዋለን፡፡ ኦርቶዶክሳዊ የድኅነት ትምህርት በቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ በጥልቀትና በስፋት ተብራርቷል፡፡ ድኅነታችን የፕሮቴስታንቱ ዓለም እንደሚለው በጸጋ ብቻ ያይደለ በእምነትና በምግባር የሚከናወን በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የሚደመደም በተጋድሎ የሚሠምር ነው፡፡

በሰሙነ ሕማማት ደረጃ በደረጃ የሚካሔዱ ሥርዐቶች አሉ እነዚህ ተግባራዊ ሥርዐቶች መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዐይነ ኅሊና እየሳልን በልቡናችን ከሊቶስጥራ እስከ ቀራንዮ እንከተለዋለን፡፡

በዕለተ ሆሣዕና የቤተ መቅደሱ በር ተዘግቶ የነገሥታት ንጉሥ የጌቶች ጌታ የሆነው አምላክ በበር ቆሞ “አርኅው ኆኀተ መኳንንት….. መኳንንት ደጆቻችሁን ክፈቱ” በማለት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ካህናተ አይሁድ የልቡናቸውን በር ቆልፈው አምላክነቱን ክደው እሩቅ ብእሲ እንደሆነ በማሰብ “ደጆቻችንን እንከፍትልህ ዘንድ አንተ ማነህ?” ማለታቸውን ለማስታወስ የዕለቱ ቀዳስያን በቤተ መቅደሱ ውስጥ ይሆናሉ፡፡

ከሆሣዕና ማግሥት ከዕለተ ሰኑይ /ሰኞ/ ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ያሉት ዕለታት የራሳቸው ስያሜ አላቸው፡፡

Read more

ሞተ ወልደ እግዚአብሔር

ፈጣሪዋ በዕንጨት መስቀል ላይ ተዘርግቶ ተሰቅሎ በአየችው ጊዜ ፀሐይ ጨለመች እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም14 የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት ሐዋርያ ጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው ነው እንዳለ ነፍሱ ከመለኮት ሳትለይ ከሥጋ ተለየች በዚያ ጊዜ ሥጋ ከመለኮት ሳይለይ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር፡፡

እንዲሁም ነፍስ ከመለኮት ጋራ አንድ ሁና እሥረኞች ነፍሳትን ትፈታቸው ዘንድ ወደ ሲኦል ወረደች፡፡

እርሱ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ ያለ ልዑለ ባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በጌትነቱ ዙፋን ተቀምጦ ያለ ለእርሱም ምስጋና የክብር ክብር ገንዘቡ የሆነ ራሱን ሠውቶ አዳነን፣ የመንግስቱን ደጆች በፈሳሽ ደሙ ከፈተልን፡፡

ሐዋርያዊ ቅዱስ አትናቴዎስ እንዳለ የእግዚአብሔር ታላቅ የማዳን ሥራ ለባሕርያዊ ደግነቱ የተገባ ነው፡፡ አንድ ንጉሥ የመሠረተው ከተማ ወይም የሠራው ቤት ከጠባቂዎቹ ስንፍና የተነሣ በሽፍታ ቢጠቃና ቢወረር ሽፍታውን ተበቅሎ ይዞታነቱን ያጸናል እንጂ በጠላት በመወረሩ ምክንያት አይተወውም፡፡ የአብ አካላዊ ቃልም የእጁ ሥራ የሆነውን የሰው ዘር ጠፍቶ እንዲቀር አልተወውም፤ ሞትን የራሱን ሰውነት ለሞት አሳልፎ በመስጠት ሲያስወግድ፣ ለሰው ተሰጥቶት፣ ነገር ግን ሕጉን በመተላለፉ ምክንያት አጥቶት የነበረውን ሁሉ በኃይሉና በሥልጣኑ መለሰ፡፡

ይህንንም በመንፈሰ እግዚአብሔር የተቃኙት የመድኀኒታችን አገልጋዮች የጻፏቸው ቅዱሳን መጻሕፍት እንዲህ በማለት ያረጋግጡልናል፡፡ ‹‹ይህን ስለ ቆረጥን የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል፤ አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፣ እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፣ በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ፡፡›› 2 ቆሮ 5÷14-15

በመቀጠልም ሌላ ማንም ሳይሆን ራሱ የእግዚአብሔር ቃል ለምን ሰው መሆን እንዳስፈለገው ምክንያቱን ይነግረናል፡- ‹‹ሁሉ ለእርሱ የሆነና ሁሉም በእርሱ ለሆነ ለርእሱ ብዙ ልጆችን ወደ ክብር ሲያመጣ የመዳናቸውን ራስ በመከራ ይፈጽም ዘንድ ተገብቶታልና፡፡›› ዕብ. 2÷9 ይህም ማለት ሰውን ከጀመረው ጥፋት መልሶ ሕይወትን መስጠት ጥንቱን ከፈጠረው ከእግዚአብሔር ቃል በስተቀር ለሌላ ለማንም ተገቢ አይደለምና፡፡

አካላዊ ቃል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን የተዋሐደው እንደ እርሱ ሰዎች ለሆኑ ሥጋውያን ሁሉ ቤዛ ይሆን ዘንድ ነበር፡፡ ሐዋርያው ‹‹ልጆቹ በሥጋና በደም እንደሚካፈሉ እርሱም እንዲሁ በሥጋና በደም ተካፈለ፤ በሞቱ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን ይሽረው ዘንድ፣ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፤ በሕይወታቸው ዘመን ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ ያወጣ ዘንድ›› ዕብ. 2÷14-15 በማለት እንደገለጸው፡፡ የራሱን ሰውነት በመሰዋት በእኛ ላይ የነበረውን ሕግ (ትሞታለህ የሚለውን) በመፈጸም አስወገደልን፡፡

Read more

ሆሣዕና (የዐቢይ ጾም 8ኛ ሳምንት)

የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)

ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዓቀብ ሀገረ እግዚአብሔር ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት ነሢኦሙ አዕፁቀ በቀልት እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም ተፅዒኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ሀገረ ኢየሩሳሌም በትፍሥሕት ወበሐሴት ይሁቦሙ ኃይለ ወሥልጣነ፡፡

ትርጉም: “በፋሲካ በዓል ሰሞን የእውነት አምላክ ደቀ መዛሙርት ወደ ደብረ ዘይት ቀረቡ፤ በሀገረ እግዚአብሔር (ኢየሩሳሌም) አቀበቱ ላይ ብዙ አረጋውያንና ሕፃናት የዘንባባ ቅጠል ይዘው ሆሣዕና በአርያም እያሉ ተቀበሉት፣ በአህያ ውርንጫ ላይ ተጭኖ በፍጹም ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። ለእነዚህ ኃይልና ሥልጣንን ይሰጣቸዋል።

መልዕክታት

ዕብ.8÷1-ፍጻ. ከተናገርነውም ዋናው ነገር ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፡፡ እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፤ እርስዋም በሰው ሳይሆን በእግዚአብሔር የተተከለች ናት፡፡

1ኛጴጥ.1÷13ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና ነቅታችሁ ኑሩ፤ ኢየሱስ ክርስቶስም ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ፡፡    

የሐዋ.8÷26-ፍጻ. የእግዚአብሔር መልአክም ፊልጶስን ተናገረው፤ እንዲህም አለው÷ “በቀትር ጊዜ ተነሣና በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚያወርደው በምድረ በዳው መንገድ ሂድ፡፡” ተነሥቶም ሄደ፡፡” እሆም÷

Read more

ኒቆዲሞስ (የዐቢይ ጾም 7ኛ ሳምንት)

የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)

ሖረ ኀቤሁ ዘስሙ ኒቆዲሞስ ወይቤሎ ለኢየሱስ ረቢ ሊቅ ንሕነ ነአምን ብከ ከመ እምኀበ አብ መጻእከ ከመ ትኩን መምህረ፤ ዕጓለ አንበሳ ሰከብከ ወኖምከ አንሥአኒ በትንሣኤከ፡፡

ትርጉም:- ስሙ ኒቆዲሞስ የተባለው ሰው ወደ ጌታችን ኢየሱስ ሄደ፤ መምሕር ሆይ ልታስተምር ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ እንደመጣህ እናምንብሃለን አለው። የአንበሳ ደቦል ተኛህ፣ አንቀላፋህም፤ በትንሣኤህ አንሣኝ።

ምንባባት/መልዕክታት/

ሮሜ.7÷1-11 ወንድሞቻችን! ሕግን ለሚያስተውሉ እናገራለሁና÷ ሰው በሕይወት ባለበት ሁሉ ሕግ እንዲገዛው አታውቁምን? ባል ያላት ሴት ባልዋ በሕይወት ሳለ ከእርሱ ጋር በሕግ የታሰረች ናት፤ ባልዋ የሞተ እንደ ሆነ ግን በሚስትነት ታስራበት ከኖረችው ሕግ የተፈታች ናት፡፡

1ኛ ዮሐ.4÷18-ፍጻ በፍቅር መፈራራት የለም፤ ፍጽምት ፍቅር ፍርሀትን ወደ ውጭ ታወጣታለች እንጂ፤ ፍርሀት ቅጣት አለበት፤ የሚፈራም በፍቅር ፍጹም አይደለም፡፡  

የሐዋ.ሥራ.5÷34-ፍጻ በሸንጎዉም በሕዝቡ ሁሉ ዘንድ የከበረ የኦሪት መምህር ስሙን ገማልያል የሚሉት አንድ ፈሪሳዊ ተነሣ፤ ሐዋርያትንም ከጉባኤዉ ጥቂት ፈቀቅ እንዲያደርጉአቸው አዘዘ፡፡ እርሱም እንዲህ አላቸው፦ Read more

ገብር ኄር (የዐቢይ ጾም 6ኛ ሳምንት)

የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)

መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወምእመን ዘይረክቦ እግዚኡ በምግባረ ሠናይ ወይሠይሞ ዲበ ኲሉ ንዋዩ ካዕበ ይቤሎ እግዚአብሔር ገብር ኄር ወምእመን ዘበውኁድ ምእመነ ኮንከ ዲበ ብዙኅ እሠይመከ ባእ ውስተ ፍሥሐሁ ለእግዚእከ፡፡

ትርጉም: ጌታው በመልካም ሥራ የሚያገኘው በሐብቱ ኹሉ ላይ የሚሾመው፤የታመነ በጎ አገልጋይ ማን ነው? ዳግመኛም እግዚአብሔር አንተ የታመንክ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ የታመንህ ስለኾንህ በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ይለዋል፡፡

ምንባባት

2ኛ ጢሞ.2÷1-15 ልጄ ሆይ÷ አንተም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ በርታ፡፡ በብዙ ምስክሮች ፊት ከእኔ የሰማኸውን ትምህርት ለሌሎች ሊያስተምሩ ለሚችሉ ለታመኑ ሰዎች እርሱን አስተምራቸው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደሚያገለግል በጎ አርበኛ ሆነህ መከራ ተቀበል፡፡ 

1ኛ ጴጥ.5÷1-11 እንግዲህ እኔ ከእነርሱ ጋር ሽማግሌ÷ የክርስቶስም መከራ ምስክር÷ ደግሞም ሊገለጥ ካለው ክብር ተካፋይ የሆንሁ በመካከላቸው ያሉትን ሽማግለዎችን እማልዳቸዋለሁ፡፡ በእናንተ ዘንድ ያሉትን የእግዚአብሔርን መንጋዎች ጠብቁ፤ ስትጠብቁአቸውም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በውድ እንጂ በግድ አይሁን፤ በበጎ ፈቃድ እንጂ መጥፎውን ረብ በመመኘትም አይሁን፡፡  Read more

ደብረ ዘይት

                                                                                                                                                                                                           በአባ ዘሚካኤል ደሬሳ

ዓለሙ ፍጻሜ ምልክቱ ምንድ ነው?/ማቴ. 24፣3/
በዓቢይ ጾም ውስጥ ካሉት ሳምንታት ደብረ ዘይት 5ኛው ሳምንት ላይ ይውላል፡፡ ደብረ ዘይት ትርጉሙ የወይራ ዛፍ ተራራ ማለት ሲሆን፣ ይህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም በሚገኘው በደብረ ዘይት ተራራ ቅዱሳን ሐዋርያት” የዓለሙ ፍጻሜስ ምልክቱ ምንድነው?”/ማቴ. 24፣3/ ብለው ጠይቀውት እርሱም የማይቀረውን የዓለም ፍጻሜና አስቀድመው የሚፈጸሙ ምልክቶችን አስረድቷቸዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ይህንኑ በደብረ ዘይት ሳምንት ታስበዋለች፤ ለምእመናኑም ከዘመኑ ሁኔታ አንጻር በመጻሕፍት የተጠቀሱትን የትንቢት ምልክቶቹን ከተግባራዊ የዓለም ክንዋኔዎች አንጻር በማገናዘብ ታስተምራለች፡፡ በመሆኑም በቤተ ክርስቲያናችን በደብረ ዘይት ሳምንት ምጽአትን አስመልክቶ የሚነገሩ ምስጢራት እጅግ ሰፊ ናቸው፡፡ ነገር ግን በዚህ ጽሑፍ በመጠኑ የምናየው ከቅዱሳት መጻሕፍት አንጻር በዓለም እየተከሰቱ ካሉ ወቅታዊ ምልክቶች ጋር በማገናዘብ ይሆናል፡፡

Read more